Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ኢትዮጵያ ለጂቡቲና ለሱዳን ከሸጠችው የኤሌክትሪክ ሃይል ከ49 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

0 468

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ኢትዮጵያ ባለፉት 10 ወራት ከኤሌክትሪክ ሃይል ሽያጭ በአጠቃላይ ከ3 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቷን የውሃ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር ገለፀ።

በ2009 በጀት ዓመት ባለፉት 10 ወራት ከኤሌክትሪክ ሃይል ለመሰብሰብ የታቀደው ከ4 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በላይ እንደነበርም ነው ሚኒስቴሩ የገለፀው።

የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ብዙነህ ቶልቻ እንደገለጹት፥ በ10 ወራት ውስጥ ከተሰበሰበው አጠቃላይ ገቢ ውስጥ ከ49 ሚሊየን 400 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በላይ ገቢው የተገኘው ለሱዳን እና ለጂቡቲ ከተሸጠ የኤሌክትሪክ ሃይል ሽያጭ ነው።

ኢትዮጵያ እየገነባቻቸው ያለቻቸው የሀይል ማመንጫዎች ሲጠናቀቁ የሀገር ውስጥ የሀይል ፍላጎትን ከማሟላት ባለፈ ለተለያዩ አገራት የኤሌክትሪክ ሀይል የማቅረብ ፍላጎት እንዳለት ይታወቃል።

ሀገሪቱ ለታንዛኒያ 400 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመሸጥ የሚያስችል ስምምነት ማድረጓም ይታወሳል።

ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ገዝተው መጠቀም የጀመሩት ሱዳን እና ጅቡቲም ተጨማሪ ኃይል ጠይቀዋል።

ኬንያም 200 ሜጋ ዋት ለመግዛት የጠየቀች ሲሆን፥ ሃይሉን ለማቅረብ የመስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክት ተፈርሞ ወደ ሥራ ተገብቷል።

በቀጣይ የጠየቁትን የኃይል ፍላጎት ለማቅረብ ተጨማሪ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ለመሥራት ጥናት እየተደረገ ነው ተብሏል።

ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት እያቀረበች ያለችው የኤሌክትሪክ ኃይል የሀገራቱን ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት በማጠናከርና የልማት ትስስሩን በማፋጠን ላይ ይገኛል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy