Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የአውሮፓ ህብረት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና ልማት የሚውል 59 ሚሊየን ዩሮ አጸደቀ

0 562

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የአውሮፓ ህብረት በአፍሪካ ቀንድ መረጋጋት ለማጠናከር ፣ህገወጥ ስደትን ለመግታት እና መፈናቀልን ለመቀነስ የሚያግዘው 59 ሚሊየን ዮሮ መመደቡን አስታውቋል፡፡

የአውሮፓ ህብረት በላከው መግለጫ ፥ ህብረቱ ለአፍሪካ ቀንድ ሀገራት የመደበው ገንዘብ ለሁሉም የቀጠናው ሀገራት ሰላም እና ልማት ፕሮጅክቶች የሚውል እንደሆነ ገልጿል፡፡

የገንዘብ ድጋፉ በቀጠናው የሰላም ግንባታ፣የጸጥታና የመረጋጋት ስራዎችን ማጠናከር ብሎም ኢኮኖሚያዊ ትስስር እና ልማትን ማሻሻልን ያለመ ነው፡፡

ከተጠቀሰው ገንዘብ ውስጥ 40 ሚሊየን  ዩሮ ለምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት /ኢጋድ/ እና ለቀጠናው ሀገራት ሰላምን ለማስፈን ለሚረዱ ቁልፍ ተግባራት የሚውል መሆኑ ተጠቅሷል፡፡

የኬኒያ ብሄራዊ ጸረ- ሽብር እንቅስቃሴ ስትራቴጂ ለመደገፍ በህብረቱ እና የኬኒያ ትብብር ማዕቀፍ 5 ሚሊየን ዩሮ ይውላል ተብሏል፡፡

ለሰሜናዊ ደርፉር 10 ሚሊየን ዩሮ የተመደበ ሲሆን ፥በዚህ ገንዘብ 80ሺህ አነስተኛ አምራቾች በቀጥታ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ እና ወደ 700 ሺህ ሰዎች በተዘዋዋሪ የሚደግፍ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የአውሮፓ ህብረት የገንዘብ ድጋፍ በቀጠናው ዘላቂ ሰላም እና ልማት በመፍጠር የሰዎች ስደትን ለመከላከል ብርቱ እገዛ እንደሚኖረው ተዘግቧል፡፡

አብዛኛው ገንዘብ የሚውለው ለስራ ፈጠራ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት በተለይ ወጣቶችን እና ሴቶችን የሙያ ስልጠናዎች በመስጠት የጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች እንዲጠናከሩ ይሆናል፡፡

ምንጭ፦አውሮፓ ህብረት

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy