Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የተለያዩ የልማት ተግባራት የሚውል የ4 ነጥብ 9 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ አደረገ

0 525

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ባንክ በአገሪቷ በአጋርነት ለሚያከናውናቸው የተለያዩ የልማት ሥራዎች የሚውል የ4 ነጥብ 9 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ አደረገ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከዓለም ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ  ክሪስታሊና ጂኦርጂቫ ጋር ተወያይተዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚዋ   ከውይይቱ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያ ዜጎቿን ከድህነት ለማላቀቅ ከዓለም ባንክ ጋር በቀጣይ ሦስት ዓመታት በአጋርነት ለምታከናውናቸው የልማት ሥራዎች የሚውል የ4 ነጥብ 9 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል።

ድጋፉ ለአፈርና ውሃ ጥበቃ፣ ለተፋሰስ ልማት፣ ለሴቶች ሥራ ፈጠራና ለሴፍቲኔት ፕሮግራም እንደሚውልም ገልጸዋል።

በድህነት ቅነሳና በሥራ ፈጠራ ላይ የተሰራውን ሥራ አድንቀው በአገሪቷ ያለውን እምቅ የፈጠራ አቅም መጠቀም እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

በተለይም በሴፍትኔት ፕሮግራም እየተከናወነ ያለው ተግባር ዜጎች ከድርቅ እንዲወጡ ብቻ ሳይሆን ህይወታቸው በዘላቂነት እንዲቀየርና እንዲሻሻል ማድረግ መቻሉ የሚደነቅ እንደሆነም ነው የገለፁት።

በቀጣይም የተለያዩ የልማት ሥራዎችን በጋራ ለመከወን ምክክር እየተደረገ መሆኑንና መግባባት ላይ ሲደረስ የድጋፉ መጠን ሊጨምር እንደሚችል አስታውቀዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በበኩላቸው አገሪቷ ድህንትን ለማሸነፍና መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት የምታደርገውን ጥረት ከዓለም ባንክ ጋር መስራቷ ለውጥ ማምጣቱንና ድጋፉ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በሴቶች ተጠቃሚነት፣ በስራ ፈጠራ፣ በትምህርት፣ በጤናና በሌሎች መሰረተ ልማቶች እንዲሁም በሴፍትኔት ፕሮግራም የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ነው የተናገሩት።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy