Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ እስማኤል ቢቂላ የክስ መዝገብ በተከሰሱ 23 ግለሰቦች ላይ ቅጣት አስተላለፈ

0 3,182

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት በእነ እስማኤል ቢቂላ የክስ መዝገብ የተጠቀሱ ሀያ ሶስት ግለሰቦች በጅማ አከባቢ እስላማዊ መንግስትን ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል በሚል የሽብር ወንጀል ክስ ከ3 እስከ 15 በሚደርስ ፅኑ እስራት ቀጣቸው።

ተከሳሾቹ  ከ2002 እስከ 2006 ዓ.ም በጅማ የተለያዩ አካባቢዎች ግብር አትክፈሉ ፣ በሸሪዓ ሕግ እንጂ በመንግስት ሕግ መመራት አያስፈልግምና  ተያያዥ ቅስቀሳዎች አድርገዋል የሚሉ ክሶች  ቀርበውባቸዋል ።

ተከሳሾቹ ፊርቃ ነጃህ የሚል የሽብር ቡድን በማቋቋም ፣ አባላት በመመልመል፣ የመለመሏቸውን አባላት ወደ ሞቃድሾ  በመላክ ከአልሸባብ ወታደራዊ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረጉን ክሳቸው ያስረዳል።

አባላቱ ያቋቋሙትን የሽብር ቡድን በገንዘብ በመደገፍ ከተለያዩ ምንጮች ፋይናንስ ከማድረግ  ባሻገር በጅማና አካባቢው ተሽከርካሪዎችን በማስቆም ንብረትና ገንዘብ ከመዝረፍ ጀምሮ አንድ ቻይናዊ እስከ መግደል ደርሰዋል ብሏል የክስ መዝገቡ።

በዚሁ መሰረት ክሱን ሲመረምር የቆየው ፍርድ ቤቱ በዛሬው እለት 1ኛ ተከሳሽ የቡድኑ ሰብሳቢ የነበረው እስማኤል ቢቅላ በአስር አመት ጽኑ እስራት ሲቀጣ በክስ መዝገቡ 18ኛ  ተራ ቁጥር ተከሳሽ የሆነው ዙበይር የተሰኘው ተከሳሽ በ15 ዓመት  ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።

በቡድኑ አጠቃላይ ክስ ተመስርቶባቸው የተፈረደባቸው ተከሳሾች 23 መሆናቸው ተመልክቷል።

ሪፖርተ:- ጥላሁን ካሳ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy