Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ዶክተር ቴድሮስ ከተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ጋር ተወያዩ

0 940

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪና  የቀድሞው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አንዋር ቢን ሞሃመድ ጋርጋሽ ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን የኤሚሬቶቹ የዜና ወኪል ዘግቧል፡፡

ዶክተር ቴድሮስ ከኢፌዴሪ መንግስት ለፕሬዝዳንት ሼክ ከሊፋ ቢን ዛይድ አል ናሂያን እንዲሁም  ለምክትላቸውና ለዱባዩ ሀገረገዥ ሼክ ሞሃመድ ቢን ራሺድ  የተላኩ ሁለት ደብዳቤዎችን ለሚኒስትር ዴኤታው አስረክበዋል፡፡

ደብዳቤዎቹ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ከማጠናከር ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን  ስለማካተታቸውም የዜና ወኪሉ ጨምሮ አስነብቧል፡፡

የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ከኢትዮጵያ የመካከለኛው ምስራቅ የንግድ አጋሮች የሁለተኝነት ደረጃን ይዛለች፡፡

እኤአ ከ2002 እስከ 2012 ባሉት ዓመታት ብቻ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ልውውጥ ከ45.4 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወደ 809 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማሻቀቡን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

ከመጋቢት – ሀምሌ 2008 ዓ.ም በነበሩት አምስት ወራት ብቻ መሰረታቸውን በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ያደረጉ 20 ባለሃብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ በልዩ ልዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች መሰማራታቸው ግንኙነቱ እያደገ ለመምጣቱ ማሳያ ነው፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy