Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ጅቡቲ በአፍሪካ ዘመናዊ ወደብ ለአገልግሎት ክፍት አደረገች

0 2,677

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ጅቡቲ በአፍሪካ ዘመናዊ የተባለውን ወደቧን ለአገልግሎት ክፍት አደረገች፡፡

“ዶራሌህ መልቲ ፐርፐዝ ፖርት” የሚል ስያሜ ያለው ይህ ወደብ ሀገሪቱ ለዓለም አቀፋዊ የመርከብ አገልግሎት ተደራሽነት የምታደርገው ጥረት አካል ነው ተብሏል፡፡

ዶራሌህ ባለብዙ አገልግሎት የወደብ መሰረተ ልማት ለጅቡቲ ለአፍሪካ የንግድ እምብርት መሆኗን ማረጋጋጫ ነው ሲሉ የጅቡቲ ወደቦች እና ነጻ ቀጠና ባለስልጣን ሃላፊው አቡበከር ኦማር ሃዲ ተናግረዋል፡፡

ዶራሌህ ወደቡ በ690 ሄክታር ላይ ያረፈ ሲሆን፥ ለግንባታውም ከ590 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ወጪ ጠይቋል፡፡

ወደቡ 752 ኪሎ ሜትር ከሚረዝመው ከአዲስ አበባ ጅቡቲ የባቡር መስመር ፕሮጀክት ጋር በተመሳሳይ ጊዜ ነው ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነው፡፡

ጅቡቲ እስያን፣ አፍሪካን፣ እና አውሮፓን በማስተሳሰር የዓለም የንግድ መስመር ማዕከል ሆናለች፡፡

አዲሱ ወደቧም ከተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች የሚመጡ 30 ሺህ መርከቦችን ተቀብሎ የማሳረፍ አቅም አለው፡፡

በዚህም ከእስያ ሀገራት 59 በመቶ፣ ከአውሮፓ 21 በመቶ ከአፍሪካ ደግሞ 16 በመቶ የንግድ እቃዎችን ያስተናግዳል፡፡

ምንጭ፡-ሲጂቲኤን

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy