Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ገንዘቤ ዲባባ በኢዩጅን የዳይመንድ ሊግ ውድድር አሸነፈች

0 524

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በአሜሪካ ኢዩጅን የአምስት ሺህ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር አሸነፈች።

ገንዘቤ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 14 ደቂቃ ከ25 ሰከንድ ከ22 ማይክሮ ሰከንድ ወስዶባታል።

ገንዘቤ ትናንት ምሽት ውድድሩ ከመካሄዱ በፊት በእህቷ ጥሩነሽ ዲባባ የተያዘውን የ5 ሺህ ሜትር የዓለም ክብረ ወሰን በመስበር ጭምር እንደሚታሸንፍ ተናግራ ነበር።

ይሁንና ገንዘቤ ውድድሩን ስታሸንፍ የገባችበው ሠዓት ክብረ ወሰኑን እሰብረዋለሁ ካለችውና ጥሩነሽ ዲባባ ካስመዘገበችው 14 ደቂቃ ከ11 ሰከንድ ከ15 ማይክሮ ሰከንድ የዓለም ክብረ ወሰን በ14 ሰከንድ የዘገየ ነው።

በትናንቱ የኡጂን የሴቶች የአምስት ሺህ ሜትር ሩጫ ገንዘቤን ተከትላ የገባችው ኬንያዊቷ ሊሊያን ካሳይት ስትሆን ውድድሩን ለማጠናቀቅ 14 ደቂቃ ከ36 ሰከንድ ከ80 ማይክሮ ሰከንድ ወስዶባታል።

ውድድሩን ሶስተኛ ሆና ያጠናቀቀችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷና የኔዘርላንድስ ዜግነት ያላት ሲፋን ሀሰን ነች።

ገለቴ ቡርቃና ደራ ዲዳ አራተኛና አምስተኛ ሆነው ውድድራቸውን አጠናቀዋል።

 

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy