Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ግዙፉ ጄነራል ኤሌክትሪክ ኩባንያ ቢሮውን በአዲስ አበባ ከፈተ

0 470

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በዓለም ግዙፉ የዲጂታል ኢንዱስትሪ ኩባንያ የሆነው ጄነራል ኤሌክትሪክ ትናንት በአዲስ አበባ ቢሮውን ከፍቷል።

በመክፈቻ ስነስርዓቱ ላይ የኢፌድሪ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ፣ በአፍሪካ የጄነራል ኤሌክትሪክ ፕሬዚዳንትና ስራ አስፈጻሚ ጃይ አየርላንድ እና በኢትዮጵያ የጄኔራል ኤሌክትሪክ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳንኤል ሃይሉ እንዲሁም ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

ፕሬዚዳንት ሙላቱ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፥ የጄነራል ኤሌክትሪክ በኢትዮጵያ ቢሮውን መክፈት፥ መንግስት ምቹ የቢዝነስ አካባቢን ለመፍጠርና የውጭ ባለሀብቶችን ለመሳብ የሚያደርገው ጥረት አንድ ማሳያ ነው።

ይህም ጥረት መንግስት ሀገሪቱ በ2025 መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለመሰለፍ የያዛቸው አገራዊ ግብ አካል ነው ብለዋል ፕሬዚዳንቱ።

ጄነራል ኤሌክትሪክ የአፍርካ የኢንቨስትመንት አጋርነቱን ለማጠናከር በተለይም ከሰሃራ በታች ባሉ 33 ሀገራት 2 ሺህ 600 ሰራተኞችን ይዞ እየሰራ ነው።

በዚህ እንቅስቃሴውም ኩባንያው በ2016 በጀት ዓመት 3 ነጥብ 9 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ አግኝቷል።

በኢትዮጵያ አዲስ በተከፈተው ቢሮው አማካኝነትም በሀገሪቱ ካሉ የግል ዘርፎች እና ኢንተርፕራይዞች ጋር በመቀናጀት የቴክኖሎጂ የእውቀት ሽግግር ስራን ያከናውናል ነው የተባለው።

በኢትዮጵያ የጀኔራል ኤሌክትሪክ ስራ አስፈጻሚው አቶ ዳንኤል ሃይሉ፥ ኩባንያው በኢትዮጵያ ስራውን ከጀመረ ዘጠኝ ዓመት ያስቆጠረ ሲሆን፥ የሰው ሃይሉን በማጠናከር ሀገሪቱ በሃይል፣ በትራንስፖርት እና በጤናው መስክ ስኬት ለማስመዝገብ በምትሰራው ስራ የበኩላችንን ለማበርከት እንሰራለን ነው ያሉት።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy