Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ምክር ቤቱ ሁለት ረቂቅ አዋጆችን አፀደቀ

0 386

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት ረቂቅ አዋጆችን ሲያፀድቅ አንድ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለዝርዝር እይታ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቷል።

በኢትዮጵያና ቻይና መንግስታት መካከል የተደረገውን በወንጀል ጉዳይ ግለሰቦችን አሳልፎ የመስጠትና በፍትሃብሄርና በንግድ ጉዳዮች ላይ የተደረጉ የትብብር ስምምነቶችን በሙሉ ድምጽ አፅድቋል።

የምክር ቤቱ የሕግ፣ ፍትህና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጴጥሮስ ወልደሰንበት እንደገለፁት፥ በወንጀል ጉዳይ ግለሰቦችን አሳልፎ ለመስጠት የተደረገው ስምምነት በሃገራቱ ሠላም፣ ፀጥታና መረጋጋትን ለማረጋጋጥ አስተዋፅኦ አለው።

ሃገሪቷ የጀመረችውን የልማትና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አጠናክራ ለማስቀጠል የሕግ የበላይነት መከበር ጉልህ ሚና ያለው በመሆኑና ወንጀል ፈፅመው ከሃገር የሚሸሹ ሰዎችን ለፍርድ ለማቅረብም ያስችላል ነው ያሉት።

የፍትሃብሄርና የንግድ ጉዳዮች ስምምነቱም በሃገራቱ መካካል እያደገ በመጣው የንግድና የፍትሃብሔር ግንኙነት አለመግባባቶች ቢፈጠሩ በቀላሉ መፍታት እንደሚያስችል ተናግረዋል።

በሃገራቱ መካከል ያሉ ተዋዋይ ወገኖች በውላቸው መሰረት ባይፈፅሙና ክርክር ቢነሳ መረጃዎች እንደ አስፈላጊነቱ ከሁለቱም ሃገራት በቀላሉ ተደራሽ እንዲሆኑም ያደርጋል ብለዋል።

የፍርድ ሂደትን ለማፋጠን በተጨማሪም የሚሸሹና የሚደበቁ የሃገርና የግለሰብ ንብረቶችን ለማስጠበቅ ታስቦ የተደረገ ስምምነት መሆኑንም አስረድተዋል።

ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወስን የወጣውን አዋጅ ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ መርምሮ፥ ለሕግ፣ ፍትህና አስተዳደርና ለንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች መርቷል።FBC

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy