Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ሳውዲ አረቢያ ህጋዊ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞችን ትቀበላለች

0 1,435

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞችን በህጋዊ መንገድ እንደምትቀበል የሀገሪቱ ሰራተኛና ማህበራዊ ልማት ሚኒስትር አሊ አል ግሃፊስ ተናገሩ፡፡

ለዚህ ያመች ዘንድም ከኢትዮጵያው የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትር አብዱልፈታህ አብዱላሂ ሀሰን ጋር ስምምነት  ተፈራርመዋል፡፡

በስምምነቱ መሰረት የኢትዮጵያ መንግሥት በሀገሪቱ ህግ መሰረት የተሰጣቸውን ስራ በአግባቡ ለማከናወን የሚያስል የተሟላ ጤና እና እውቀት ያላቸውን እንዲሁም ከወንጀል ነጻ የሆኑ  ሰራተኞችን ብቻ ለመላክ ከስምምነት ላይ ደርሷ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰራተኞቹ በሀገር ውስጥ አስፈላጊውን ስልጠና መስጠትና የሳውዲ አረቢያን የሥራ ባህርይ፣ ባህልና ህግ  የማስገንዘብ ሃላፊነቱን ወስዷል፡፡

ስምምነቱ የሁለቱን ሀገራት ትብብር ከማጠናከሩም በላይ የሰራተኞችንና የአሰሪዎችን መብቶች ለማስከበርና የአሰሪና ሰራተኛ ውሉን ተፈጻሚነትም ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ የሰራተኛና ማህበራዊ ልማት ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

የሰራተኛ ምልመላውንም ህጋዊ ፈቃድ ባላቸው ድርጅቶች አማካኝነት ብቻ ለማከናወን ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ሰራተኛቹ ወደ ስራ ከመሰማራታቸው በፊት የሀገሪቱን ህግና ስርዓት ለማስገንዘብ  የሚያስችሉ ስራዎችን ለመስራት ዝግጁ መሆኑን የኤፌዴሪ ሰራተኛና ማህበራዊ ሚኒስትር አረጋግጠዋል፡፡

በአሰሪና ሰራተኛ አገናኝ ድርጅቶች በኩል የሚቀርቡ ሰነዶችን የማረጋገጥ ስራ እንደሚሰራም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት፡፡

ስምምነቱ በስራ ውሉ መሰረት አሰሪዎቹ ለሰራተኞቹ በሚከፈቱ የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች አማካኝነት ደመወዛቸውን ወደየሀገራቸው ለማስተላለፍ እንደሚያስችላቸውም የሀገሪቱ ጋዜጣ አስነብቧል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy