Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በትግራይ ክልል ለወጣቶች ፈንድ ከቀረቡ 43 ሺህ ቢዝነስ ፕላኖች መካከል 2 ብቻ ተግባራዊ መሆናቸው ተገለጸ

0 487

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በትግራይ ክልል ለወጣቶች ፈንድ ተብሎ በተዘጋጀው መርሐግብር ከቀረቡት 43 ሺ ቢዝነስ ፕላኖች መካከል 2 ብቻ ወደ ተግባር መሸጋገራቸው ተገለጸ።

ቢዝነስ ፕላን ያቀረቡ ወጣቶች ለፋና ብሮድካስቲነግ ኮርፐሬት እንደተናገሩት ፥ቢዝነስ እቅዶቻቸውን ለሚመለከተው አካል ቢያቀርቡም በአፋጣኝ ወደ ተግባር ለመሸጋገር በአገልግሎት አሰጣጥ ችግር እየደረሰባቸው መሆኑን ገልፀዋል።

በተለይ ለስራ አጥ ወጣቶች የሚጠየቁት የብድሩን 10 በመቶ ቁጠባ በጣም እንደከበዳቸውም ነው የተናገሩት፡፡

የትግራይ ክልል ጥቃቅንና ኣነስተኛ ኢንተርፕራይዝ የከተሞች ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ሃይላይ አረጋዊ በበኩላቸው ፥በትግራይ የስራ አጥ ወጣቶችን ችግር ለመፍታት ስልጠናዎች እንደተሰጠ እና እንዲደራጁ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

እስከ አሁን በትግራይ ክልል ለወጣቶች ፈንድ ተብሎ በተዘጋጀው መርሐግብር ከቀረቡት 43ሺ ቢዝነስ እቅዶች መካከል 2 ብቻ ወደ ተግባር እንደተሸጋገሩ ነው የተናገሩት::

የኤጀንሲው ኃላፊ አቶ ሃይላይ እንዳሉት ፥10 በመቶ መቆጠብ የማይችሉ ስራ አጥ ወጣቶች ሳይቆጥቡ እስከ 30 ሺ ብር ብድር የሚያገኙበት ስርአት ተዘርግቷል።

ወጣቶቹ ወደ ስራ ያልገቡበትን  ምክንያቶች እና ችግሮች በመለየት  በግንቦት ወር 70 በመቶ ስራዎችን  ለመፈፀም መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል፡፡

 

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy