Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በኢሬቻ በዓል ላይ ሁከት በማስነሳት ለ55 ሰዎች ሞት ምክንያት ናቸው የተባሉ ግለሰቦች ክስ ተመሰረተባቸው

0 348

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በኢሬቻ በዓል ላይ ከሃገር ሽማግሌዎች ማይክ በመቀማትና ሁከት በማስነሳት ለ55 ሰዎች ሞት ምክንያት ናቸው የተባሉት ሁለት ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተባቸው።

ተከሳሾች ቱፋ መልካ እና ከድር በዳሶ ሲሆኑ፥ ክሱ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የወንጀል ችሎት ነው የቀረበባቸው።

የጠቅላይ አቃቢ ህግ ክስ እንደሚያመለክተው፥ 1ኛ ተከሳሽ ቱፋ መልካ በኢሬቻ በዓል ወቅት የሃገር ሽማግሌዎች ንግግር ሲያደርጉ ማይክ በመቀማት ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር በዓሉን አደናቅፏል።

2ኛ ተከሳሽ ከድር በዳሶ በበኩሉ ከመድረክ ጀርባ በመሆን በስልክ አመፁን ሲያስተባብር እንደነበር የአቃቢ ህግ ክስ ያስረዳል።

ተከሳሾቹ በወቅቱ በበዓሉ በተፈጠረው ግርግር ህይወታቸው ላለፈ 55 ሰዎች ሞት ምክንያት መሆናቸውም በክሱ ተዘርዝሯል።

ከሳሽ አቃቢ ህግም የሽብር ወንጀል ድርጊት በመፈጸም ክስ አቅርቦባቸዋል

ተከሳሾቹ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የወንጀል ችሎት ቀርበው ክሳቸው ተነቦላቸዋል።

ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹን የክስ መቃወሚያ ለመስማትም ለግንቦት 24 ቀን 2009 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

 

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy