Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ቻይና ለአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ 260 ሚሊዮን ዶላር ብድር ሰጠች

0 347

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ቻይና ለአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ 260 ሚሊዮን ዶላር ብድር ሰጠች።

በጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የተመራ የልዑካን ቡድን ከግንቦት 7 ቀን 2009 ዓ.ም ጀምሮ በቻይና የተለያዩ ግዛቶችን በመጎብኘት ላይ ነው።

ከቻይና ኤግዚም ባንክ በብድር የተገኘው ገንዘብ በአዳማ ከተማ ለሚገነባው ኢትዮ – ሁናን ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚውል ነው።

ብደሩ የተገኘው በሁለቱ ሀገራት መሪዎች በተፈረመ የሁለትዮሽ የመግባቢያ ሰነድ መሰረት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም በብድር ስምምነቱ ወቅት እንደገለጹት፤ ፓርኩ የከባድ ማሽኖች፣ የኃይል ቁሳቁሶችን የሚያመርትና ለአገሪቷ ልዩ ሊሆን የሚችል ነው።

በተለይም ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ የሚያስችላት ልዩ ፓርክ እንደሚሆን ነው የገለጹት።

“የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት፣ የሃይል ማመንጨትና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ፣ በማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ልማትና የቴክኖሎጂ እውቀት ሽግግርን ከመፍጠር አኳያ አስደናቂ ስራ እያከናወኑ ነው” ብለዋል።

በዚህም ኢትዮጵያ ከሁናን ግዛት በዘመናዊ ግብርና፣ የኢንዱስትሪ ሽግግር እና በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማትና አስተዳደር ዘርፍ ልምድ እንደምተቀስም ነው የተናገሩት።

የቻይናዋ ሁናን ግዛት በቤልት ኤንድ ሮድ ኢንሺዬቲቭ አማካኝነት በአለም አቀፍ ቀላልና ዘመናዊ የትራንስፖርት ስርዓት ዘጠኝ ፓርኮችንና 11 ቢሮዎችን ትከፍታለች።

የሁናን ግዛት ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የተለያዩ ማበረታቻዎች የቀረቡላቸው ሲሆን፤ እኤአ 2016 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ በተለያዩ ዘርፎች የ180 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ማካሄዳቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy