Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ቻይና ያለገደብ የሚታደርገው የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ታዳጊ አገራትን እየጠቀመ ነው-ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም

0 375

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የአለምን ዋነኛ ተግዳሮት ለማቃለል በዕኩልነትና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የአገራት ትስስር እንዲጠናከር ቻይና ጥሪ አቀረበች፡፡

ቻይና የአፍሪካና የኢሲያና የአውሮፓ አገራትን በመሰረተ ልማት ለማስተሳሰር ይፋ ያደረገችው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም በቤጂንግ ተጀምሯል፡፡

በጉባኤው መክፈቻ ላይ የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ጥንት የአገራትን የንግድ መስመር መነሻ በማድረግ የተጠነሰሰው መርሃ ግብር የአለም አገራትን ህዝቦችን በተለይ ታዳጊ አገራትን በጋራ ተጠቃሚነት የዕድገት ጉዞዋቸውን ለማፋጠን ትልቅ አቅም እንዳለው ገልጸዋል፡፡

ቻይና ለዚህ ቁርጠኛ አቋም በመያዝ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነች መሆኗን ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል፡፡

ጠ/ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ቻይና ያለገደብ የሚታደርገውን የጋራ ተጠቃሚነት መርህ የታዳጊ አገራትን ማነቆ ለመፍታት ከፍተኛ ሚና እያበረከተ መሆኑን ገልጸው ኢትዮጵያም ለአላማው ተፈጻሚነት የበኩሏን ድርሻ እንደምትወጣም ተናግረዋል፡፡

በቤጂንግ በተጀመረው በቤልት ኤንድ ሮድ ጉባኤ ከ100 በላይ አገራት የተወጣጡ መሪዎች የከፍተኛ ባለስጣናትና እንዲሁም የተቋማት መሪዎች ተሳታፊ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy