Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ኢትዮጵያ ለአለም ጤና ድርጅት ዋና ፀኃፊነት እንድትመረጥ ግብጽ ትደግፋለች

0 469

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴድሮስ  አድሃኖም   ከምርጫ    ቅስቀሳው ጋር  በተያያዘ  ለሁለት  ቀናት የስራ   ጉብኝት   ካይሮ   ገብተዋል፡፡

ዶ/ር ቴድሮስ  ካይሮ  አለም አቀፍ  አየር  ማረፊያ   ሲደርሱ  የሀገሪቱ  የውጭ  ጉዳይ   የአፍሪካ  ጉዳዮች ምክትል ሚኒስትር  ሞሃመድ   ኢድሪስ    አቀባበል   አድርገውላቸዋል፡፡

ከውጭ  ጉዳይ  ሚኒስትሩ  ሳሜህ  ሹክሪ   በሞሃምድ   ኢደሪስ   በኩል ለቴወድሮስ  አድሃኖም  ሰላምታ  ማድረሳቸው ተገልጿል፡፡

ኢትዮጵያ  አፍሪካን  ወክላ  ለአለም ጤና  ድርጅት  ዋና  ጸኃፊነት   ለምታደርገው  የምርጫ  ፉክክር  ሀገራቸው  ግብጽ  ድጋፍ  እንደምታደርግም ለቴድሮስ  አድሃኖም  መልዕክታቸውን  አስተላልፈዋል፡

የውጭ  ጉዳይ  ሚኒስትሩ  ከምርጫው  ጋር  በተያያዘ  ወደ  ጀኔቫ  ለሚያቀናው  የግብጽ  ልዑክ ለኢትዮጵያ  ድምጽ   እንዲሰጥም  አሳስበዋል፡፡

በኢትዮጵያ   አፍሪካን   ወክላ  ለአለም  ጤና  ድርጅት ዋና  ፀኃፊነት  ከተመረጠች   የአህጉሪቱን  ጥቅም  እንደምታስከብር  ተናግረዋል፡፡

የመጨረሻው  ምርጫ  በጀኔቫ  ግንቦት  15 እንደሚደረግም ታውቋል፡፡

ምንጭ፡- http://www.egyptindependent.com

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy