Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የሲንጋፖር ም/ ጠቅላይ ሚንስትር ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው

0 363

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የሲንጋፖር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ቲዎ ቺ ሀን በቀጣይ ሳምንት ኢትዮጵያን እንደሚጎበኙ የሲንጋፖር ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

ጉብኝቱ የአገራቱን የሁለትዮች ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ቲዎ ቺ ሀን ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ምክትል ጠቅላይሚንስትር  ደመቀ መኮንን ጨምሮ ከሌሎች የአገሪቱ ከፍተኛ ባለስለጣናት ጋር ተገናኝተው እንደሚመክሩ ገልጿል፡፡

በኢትዮጵያ ኢንቨስት ካደረጉ የሲንጋፖር ኩባንያዎችም ጋር እንደሚገናኙ የሲንጋፖሩ ስትሬት ታይም ዘገባ ያስረዳል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ቲዎ ቺ ሀን ከኢትዮጵያ በመቀጠል ደቡብ አፍሪካን እንደሚጎበኙ ከዘገባው ለመረዳት ተችሏል፡፡

ምንጭ፤ ስትሬይት ታይምስ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy