Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የቀድሞ የአርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንትና ዋና ጸሐፊ በእስራት ተቀጡ

0 783

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባላት ለሆኑና አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ለሚኖሩ ቤት ለሌላቸው አርበኞች የሰጣቸውን የጋራ መኖሪያ ቤቶችን፣ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል ተብለው የቀድሞ የማኅበሩ ፕሬዚዳንትና ዋና ጸሐፊ በስድስት ወራት ጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ ተወሰነ፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሐሙስ ሚያዝያ 26 ቀን 2009 ዓ.ም. በሰጠው ውሳኔ እንዳስታወቀው፣ የጥንታዊ ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት በነበሩት ሊቀ ትጉኃን አስታጥቄ አባተና የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ በነበሩት አሥር አለቃ ሰጥአርጌ አያሌው፣ ስድስት የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለማኅበሩ አባላት ሳይሆን ለግል ዘመዶቻቸው መስጠታቸውን ዓቃቤ ሕግ  በሰነድና በሰው ማስረጃ አረጋግጧል፡፡

ሊቀ ትጉኃን አስታጥቄ ለራሳቸው ከመውሰዳቸውም በተጨማሪ ለእህትና ለወንድማቸው መውሰዳቸውን፣ ዋና ጸሐፊውም ለራሳቸውና ለሌላ ሰው ማስተላለፋቸውን ፍርድ ቤቱ ገልጿል፡፡

ሁለቱም ተከሳሾች ሚያዝያ 24 ቀን 2009 ዓ.ም. ጥፋተኛ በመባላቸው የቅጣት ማቅለያ አቅርበው፣ እያንዳንዳቸው አምስት አምስት ማቅለያ ተይዞላቸው ነበር፡፡ በዚህም ጥፋተኛ በተባሉበት የቅጣት እርከን እያንዳንዳቸው ስድስት ወራት ጽኑ እስራትና 1,500 ብር እንዲቀጡ ውሳኔ በመሰጠቱ፣ ወደ ማረሚያ ቤት ተልከዋል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy