Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አራት ምክትል ፕሬዚዳንቶቹን ከሀላፊነት አነሳ

0 624

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አራት ምክትል ፕሬዚዳንቶቹን ዛሬ ከሀላፊነት አንስቷል።

የባንኩ የኮርፖሬት ማስተዋወቅና ግንኙነት ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ ሀይሉ ምስጋናው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳሉት፥ የሊዝ ፋይናንስ እና ቅርንጫፎች ስራ ምክትል ፕሬዚዳንት ከሆኑት አቶ ተሾመ ዓለማየሁ በስተቀር ሌሎቹ አራት የባንኩ ምክትል ፕሬዚዳንቶች ከሀላፊነታቸው ተነስተዋል።

ከሀላፊነታቸው በተነሱት አራት ምክትል ፕሬዚዳንቶች ምትክም የባንኩ ፕሬዚዳንት ጌታሁን ናና አዳዲስ ምክትል ፕሬዚዳንቶችን ሾመዋል።

በዚህ መሰረት አቶ ጌታቸው ዋቄ የፕሮጀክት ፋይናንስ ምክትል ፕሬዚዳንት፣ አቶ ሃይለእየሱስ በቀለ የብድር አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት፣ አቶ ሃዱሽ ገብረእግዚአብሄር የኮርፖሬት አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት እና አቶ እንዳልካቸው ምህረቱ የፋይናንስና ባንኪንግ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን ተሾመዋል።

በቅርቡ ለባንኩ አዲስ ፕሬዚዳንት መሾሙን ተከትሎ የተዘጋጀ አዲስ መዋቅርን መሰረት በማድረግ ምክትል ፕሬዚዳንቶቹ ተነስተዋል ነው የተባለው።

ተቋሙ በለውጥ ሂደት ውስጥ በመሆኑና ለዚህ አዲስ አደረጃጀት እየሰራ መሆኑም ለምክትል ፕሬዚዳንቶቹ መነሳት ምክንያት ነው ተብሏል።

እንደ አቶ ሃይሉ ገለጻ ባንኩ አደረጃጀቱን በአዲስ የሰው ሃይል ማሟላት በማስፈለጉ ምክትል ፕሬዚዳንቶቹ ከሃላፊነታቸው ተነስተዋል።

ለተሰናባቾቹ ምክትል ፕሬዚዳንቶች የደረሰው ደብዳቤም ለአገልግሎታቸው ምስጋናን ያካተተ መሆኑ ተመልክቷል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy