Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከሳዑዲ የሚመለሱ ዜጎችን ሁኔታ በስፍራው ተገኝተው እየገመገሙ ነው

0 259

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ከሳዑዲ ዓረቢያ የሚመለሱ ዜጎችን ሁኔታ በስፍራው ተገኝተው እየገመገሙ ነው።

በእርሳቸው የተመራው የአስቸኳይ ጊዜ ግብረ ሃይል ወደ ሳዑዲ አምርቷል።

ልዑኩ ከሳዑዲ የሚመለሱ ኢትዮጵያውያን የጉዞ ሰነድ የሚያገኙባቸውን እና የሰነድ አሰጣጥ ሂደቱን እየገመገመ ሲሆን፥ እስካሁንም በሁለት ማዕከላት በመገኘት አጠቃላይ ሂደቱን ገምግሟል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በሳዑዲ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር እንደተገናኙም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ዶክተር ወርቅነህ ዛሬ ምሽት ከሳዑዲ ዓረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለስልጣናት ጋር እንደሚመክሩ ይጠበቃል፡፡

መንግስት አዋጁ የሚመለከታቸው በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ፥ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚመራ የአስቸኳይ ጊዜ ግብረ ሃይል አቋቁሞ እየሰራ ነው።

እስከ ዛሬ በተከናወኑ ስራዎች ወደ ሀገራቸው የተመለሱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ግን ከሚጠበቀው አኳያ አነስተኛ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ኢትዮጵያውያኑ የምህረት አዋጁ ቀነ ገደብ ሳይጠናቀቅ፥ ወደሀገራቸው እንዲመለሱም መንግስት ጥሪ እያደረገ ገኛል፡፡

የሳዑዲ ዓረቢያ መንግስት በሀገሪቱ ያሉ የመኖሪያ እና የስራ ፍቃድ የሌላቸው የውጭ ሀገራት ዜጎች ለቀው እንዲወጡ ካለፈው መጋቢት 21 እስከ መጭው ሰኔ 20 ቀን 2009 ዓ.ም ድረስ የዘጠና ቀናት የምህረት አዋጅ አውጇል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy