Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የዓለም የፕሬስ ነፃነት ቀን በኢትዮጵያ እየተከበረ ነው

0 311

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የዓለም የፕሬስ ነፃነት ቀን በኢትዮጵያ በመከበር ላይ ይገኛል።

ቀኑ የተለያዩ የመንግስት እና የግል ሚዲያ ተቋማት ባለሙያዎች እና ተወካዮች በተገኙበት ነው በአዲስ አበባ ከተማ በመከበር ላይ የሚገኘው።

በዝግጅቱ ላይም የፕሬስ ነፃነት በኢትዮጵያ፣ የመገናኛ ብዙሃን ችግሮች እና አማራጮች የሚል ፅሁፍ ቀርቦም ውይይት እየተደረገበት ነው።

በውይይቱ ላይም የመገናኛ ብዙሃን ከወገንተኝነት በፀዳ መልኩ መረጃን በማድረስ መልኩም ችግሮች እንደሚስተዋሉባቸው ተነስቷል።

ለግሉ መገናኛ ብዙሃን ከመንግስት የሚደረግላቸው ድጋፍ አነስተኛ መሆኑ እና የግል የመገናኛ ብዙሃን ቁጥር አነስተኛ መሆን ላይ ውይይት እየተደረገባቸው ነው።

የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሀላፊ ሚኒስትር ዶክተር ነገሪ ሌንጮ፥ በሀገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን ታሪክ ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ ነው፤ ሆኖም ግን በህገ መንግስቱ ከከላ አግኝቶ መንቀሳቀስ ከጀመረ ሁለት አስርት ዓመታትን ብቻ ማስቆጠሩን አንስተዋል።

ዘርፉ አሁንም ቢሆን ከእውቀት እና ከክህሎት ጋር ተያይዞ ክፍተቶች ስለሚስተዋልበት የሚፈለገው ደረጃ ላይ ማድረስ አልተቻለም ሲሉም ተናግረዋል።

መገናኛ ብዙሃን የተሟላ ሙያዊ ስነ ምግባር እንዲሁም ሙያዊ እውቀት እና ክህሎት እንዲኖራቸው በስፋት መሰራት እንዳለበትም ገልጸዋልል።

የግልም ሆነ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በተጨባጭ መረጃ ላይ በመመስረት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በማጋለጥ በዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸውም ጥሪ አቅርበዋል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy