Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

40 ሺህ ሰዎች ከሳዑዲ አረቢያ ለመመለስ የጉዞ ሰነድ ወስደዋል

0 442

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ቁጥራቸው 40 ሺህ የሚደርሱ ሰዎች ከሳኡዲ አረቢያ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ የጉዞ ሰነድ መውሰዳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ መለስ አለም፥ የተመላሾችን ጉዳይ ለማፋጠን የሚያስችል ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በሳዑዲ አረቢያ ተመላሾችን ጉዳይ በፍጥነት ለማከናወን ያስችል ዘንድም 12 ዲፕሎማቶች በዛሬው እለት ወደ ስፍራው መላካቸውንም ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል።

በስፍራው ለሶስት ቀናት ጉብኝት ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ውርቅነህ ገበየሁ ከትራንስፖርት ጋር ተያይዞ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም ጋር መነጋገራቸውንም ገልጸዋል።

የአየር መንገዱ ስራ አስፈጻሚም ተጨማሪ አውሮፕላኖችን ለመመደብ እንዲያስችል በስፍራው ያለውን ሁኔታ የሚያጠና የባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው ለመላክ መስማማታቸውንም አቶ መለስ አስታውቀዋል።

ከዚህ በተጨማሪም እዛ ሀገር ለወለዱ እና ለልጆቻቸው የዘረመል (ዲ.ኤን.ኤ) ምርመራ ለሚያስፈልጋቸው ምርመራው በአጭር ጊዜ እንዲከናወን ከሳኡዲ አረቢያ መንግስት ጋር ከስምምነት ላይ መድረሱን ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል የሰራተኛ እና አሰሪ ስምምነት መፈረሙም አሁን ከሀገሪቱ እየወጡ ሰዎች ህጋዊ በሆነ መንገድ ተመልሰው እንዲሄዱ የሚኖረው አስተዋዕኦው ከፍተኛ ነው ብለዋል።

ሚኒስቴሩ በቀጣይም መሰል ስመምነቶችን ለመፈፀም እንደሚሰራም ተናግረዋል።

በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሳዑዲ አረቢያ የገቡ እና ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ዜጎች ቀነ ገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ቃል አቀባዩ ጥሪ አቅርበዋል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy