Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የሆሊውድ ኮከቧ አንጀሊና ጆሊ ከቤተሰቦቿ ጋር ኢትዮጵያን ልትጎበኝ ነው

0 1,268

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

  • ኢትዮጵያዊት ልጅ ያገኘችበትን ቀን ታከብራለች

የሆሊውድ ኮከቧ አንጀሊና ጆሊ ከ12 ዓመታት በፊት ከኢትዮጵያ በማደጎ የወሰደቻትን ዘሃራ ጆሊ ፒትና ሌሎች ልጆቿን በመያዝ ኢትዮጵያን ልትጎበኝ መሆኑን ሆሊውድላይፍ በድረ ገጹ አስፍሯል፡፡

አንጀሊና ጆሊና ከቀድሞ ባለቤቷ ከብራድ ፒት ጋር ሰኔ 29 ቀን 1997 ዓ.ም. ኢትዮጵያ በመምጣት፣ የዘሃራ እናትና አባትነትን ሲያገኙ ዘሃራ የስድስት ወር ጨቅላ ነበረች፡፡

አንጀሊና የዘሃራ እናት የሆነችበትን ቀን ለማክበርና ለዘሃራም አገሯን ለማስተዋወቅ የምትመጣ ሲሆን፣ አባቷ ብራድ ፒት ግን የማይመጣ መሆኑን ሰለብሪቲ ኢንሳይደር ጽፏል፡፡

የትዳራቸውን ውዝግብ ተከትሎ በአንጀሊና በኩል የጉዞ ጥሪ ያልተደረገለት ብራድ ፒት፣ በዘሃራ ዕድሜ ሙሉ ዘሃራን አባት ሆኖ ማሳደጉ ተገልጿል፡፡

የአንጀሊናና የብራድ ልጆች ከሆኑት ዘሃራና ሺሎህ አባታቸው አብሯቸው ቢጓዝ ደስተኛ እንደሚሆኑ መናገራቸውም ተዘግቧል፡፡

አንጀሊና ከሦስት አገሮች በመውሰድ የምታሳድጋቸውን ሦስት ልጆቿ አገራቸውን እንዲያውቁ የማድረግ ልምድ ያላት ሲሆን፣ ከዚህ ቀደምም የ15 ዓመት ልጇን ማዶክሰን ካምቦዲያ ወስዳ አገሩን አስጎብኝታዋለች፡፡

ዘሃራን ይዛ የምትመጣው ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ዘሃራን አገሯን  ባለማስጎብኘቷ ተወቅሳ ነበር፡፡ አንጀሊና በማደጎ ልጇን ዘሃራን ያገኘችበትን ሰኔ 29 ቀን 2009 ዓ.ም. ለማክበር ቀድማ ኢትዮጵያ የምትመጣ መሆኑ ተነግሯል፡፡

አንጀሊናና ብራድፒት ሦስት የአብራክ ክፋይ ልጆች ያላቸው ሲሆን ሁለቱ መንታዎች ናቸው፡፡ ከካምቦዲያ፣ ከኢትዮጵያና ከቬትናም የወሰዷቸው ሦስት የማደጎ ልጆችም አሏቸው፡፡reporter

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy