Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በስሚንቶ ስር የተደበቀ ሺሻ ተያዘ

0 1,510

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የአዳማ ቅርንጫፍ ስሚንቶ በጫነ ተሽከርካሪ ተደብቆ ሊያልፍ የነበረ 215 ሺህ ብር ግምት ያለው ሺሻ መያዙን አስታወቀ።

የቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቱ የህግ ማስከበር የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ለታ እንደገለፁት የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-45423 አ.አ በሆነ አይሱዙ የጭነት መኪና ከላይ ለሽፋን ከጫነው 40 ከረጢት ሲሚንቶ ስር ደብቆ ሊያሳልፍ የነበረው 2 ሺህ 156 ስቴካ ሺሻ ተይዟል።

ህብረተሰቡ በሰጠው ጥቆማ መሰረት ሽሻውን የጫነው ተሽከርካሪ ሰኔ 1/2009 ዓ. ም ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት አዳማ ከተማ ውሰጥ በጉምሩክ ሰራተኞችና በፌደራል ፖሊስ አባላት አማካኝነት ሊያዝመቻሉም ተገልጿል።

በወቅቱ አሽከርካሪው ከቆመበት ስፍራ መኪናውን አስነስቶ በፍጥነት ለማመለጥ በመሞከሩ የተሽከርካሪውን ጎማ ለመመታት በተተኮሰ ጥይት ግራ ጎኑን ተመቶ በአዳማ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገለት መሆኑን አስተባባሪው ተናግረዋል።

በተመሳሳይም በአዳማና ቢሾፍቱ ከተሞች ባለፉት አምስት ቀናት ውስጥ 673 ሺህ 303 ብር ግምት ያለው የኮንትሮባንድ ዕቃ መያዙን አመልክተዋል።

ለህዝብ ጤናና ለአገር ኢኮኖሚ ስጋት እየሆነ የመጣውን የኮንትሮባንድ እንቅሰቃሴ ለመግታት በሚደረገው ጥረት የህብረተሰብ ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ መቅረቡን  ኢዜአ ዘግቧል። EBC

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy