Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ከ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አልማ አስታወቀ

0 649

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ባለፉት 5 ዓመታት ከ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን የአማራ አቀፍ ልማት ማህበር (አልማ) አስታወቀ።

ማህበሩ 12ኛ መደበኛ ጉባኤውንና 25ኛ ዓመት የብር ኢዩቤልዩ በዓሉን በባህር ዳር እያከበረ ነው።

የማህበሩ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ብስራት ጋሻው ጠና እንደገለጹት፥ ማህበሩ በከልሉ እየተከናወኑ ላሉ የመሰረተ ልማት ስራዎች አጋር ሆኖ እየሰራ ነው።

ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥም የአባላቱን ቁጠር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ወደ 4 ነጥብ 1 ሚሊየን ማድረስ ችሏል ነው ያሉት ዋና ስራ አስፈጻሚዋ።

ከአባላትና ከአጋር አካላትም ባለፉት 5 ዓመታት ወስጥ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉም ተገልጿል።

በቀጣይም ማህበሩ በሚያከናውናቸው የልማት ስራዎች ሁሉም ባለደርሻ አካላት ድጋፋቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል ወይዘሮ ብስራት ጋሻው ጠና።

 

በሙሉጌታ ደሴ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy