Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የኦሮሚያ ክልል ከ 1 ሺህ በላይ የጤና ባለሙያዎችና አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ

0 432

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ጤና ጣቢያዎችና ሆስፒታሎች በአገልግሎት አሰጣጥ ችግር የታየባቸው ከ1 ሺህ በላይ የጤና ባለሙያዎችና አመራሮች ላይ እርምጃ መወሰዱን የክልሉ ጤና ጥበቃ ቢሮ ገለጸ፡፡

በጤናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ከቢሮው ጀምሮ እስከ ወረዳ ባሉ የጤና ተቋማት፥ በተደረገ ግምገማ ችግር ያለባቸውን አመራሮችና ባለሙያዎች በመለየት እርምጃ ተወስዷል።

ባለፉት አራት ወራት ከ1 ሺህ የሚበልጡ የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎችና የጤና ባለሙያዎች ላይ፥ ከቦታ ማንሳት ጀምሮ የሙያ ዲሲፕሊን ቅጣት፣ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን የየክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ አስታውቀዋል።

እርምጃ ከተወሰደባቸው መካከል ከ80 በመቶ በላይ የሚሆኑት፥ በአገልግሎት አሰጣጥ ህዝብን ያማረሩ የጤና ባለሙያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የኪራይ ሰብሳቢነት ተግባራት፣ የሙያዊ የስነ ምግባር ጉድለት፣ የመድሃኒትና ህክምና መሳሪያዎች አቅርቦትና የጥራት ችግሮች የክልሉ የጤና ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ የሚፈለገውን ያህል እንዳይሆን ማድረጋቸውን ዶክተር ደረጀ ጠቁመዋል፡፡

እየተወሰደ ካለው የማስተካከያ እርምጃ ጎን ለጎን በነባር የጤና ተቋማት የሚታየውን የቁሳቁስ ችግር ለመፍታትና አዳዲሶቹን ስራ ለማስጀመር ከ2 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተለያዩ ተግባራት ተከናውኗል፡፡

በተለይ 10 አዲስ የመጀመሪያ ደረጃና ሪፈራል ሆስፒታሎችን በውስጥ ቁሳቁስና በሰው ሃይል በማደራጀት ሥራ እንዲጀምሩ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ሌሎች በክልሉ የሚገኙ ነባር ጤና ተቋማትንም በመድሃኒት፣ በህክምና መሳሪያና የውስጥ ቁሳቁስ በማሟላት የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጡ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ምንጭ፡-ኢዜአ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy