Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የዘንድሮ የሓጂ ጉዞ ታሪካዊ የኣል ነጃሺ መስጂድ በመጎብኝት ይሆናል

0 1,000

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የዘንድሮ የሓጂ ጉዞ ታሪካዊ የኣል ነጃሺ መስጂድ በመጎብኝት ይሆናል

ከያዝነው አመት ጀምሮ ወደ  መካ የምደረግ ሃይማኖታዊ የሓጂ ጉዞ ታሪካዊ የኣል ነጃሺ መስጂድ በመጎብኝት ይሆናል። በያዝነው አመት ከነሃሴ 01/2009 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ኣስር ቀናት በሚደረገው የሓጂ ጉዞ፤ የሃይማኖቱ ምእመን ከመላው ሃገሪቱ በኣል ነጃሺ መስጂድ በመጋናኘት በአለም የመጀመርያ የእስልምና ሃይማኖት ኣማኞች ያረፍበቱን ቅዱስ ደርሒ ፆሎት በማድረግና በመጎብኘት በቀጥታ በመቐለ ከተማ ከሚገኘው የኣሉላ ኣባነጋ የአየር ማረፍያ ሜዳ በመነሳት ወደ መካ ይሄዳሉ።

ከሃገረ ሱዳን የመጡ ልኡካን በኣልነጃሺ የሚገኝ ደርሒ/የቅዱሳን መቃብር/ ፆሎት እያደረጉና እየጎበኙ

ይህ ውሳኔ የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ፣ የኢትዮጵያ  የእስልምና ጎዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ኣየር መንገድ በመተባበር ተግባራዊ ይሆናል። ከያዝነው አመት የሚጀምረው ይህ ስራ በተጣናከረ መንገድ ቀጣይነት ተጠናክሮ የሚቀጥል የሓጂ እና የዑምራ ጉዞዎች እንደሚነሩ የጋራ ኮሚቴው ገልፀዋል።

በመቐለ ከተማ የሚገኙ የኣገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና ኣስጎብኚ ድርጅቶች እንግዶቻቸውን በሚያስደስትና ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ይዞት የጠበቀ ኣቀባበል ለማድረግ በዝግጅትላይ ናቸው።

ይህ ታሪካዊ ውሳኔ የትግራይ ክልልን የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ወደላቀ ደረጃ የሚያሸጋገር እና ቱሪዝም ፍሰት በማስፋት ሃገራችን ከዚህ ዘርፍ ተጠቃሚነቷ የሚያረጋግጥ ጥሩ ጅምር ነው።

ጅምሩ በሚቀጥሉት ተከተታታይ አመታት ከአፍሪካ እና ከመላው አለም ወደ መካ የሚያደርጉት የሓጂ እና የዑምራ ጉዞዎች የኣል ነጃሺ መስጂድን እንደ ዋነኛ መዳረሻቸው በመውሰድ መሸጋገርያቸው/ትራዚት/ ለማድረግ ተጠናክሮ ይቀጥላል።

በልማት ላይ ያለ የኣልነጃሺ መስጂድ በከፊል

 

የትግራይ ባህል ቱሪዝም ቢሮ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy