Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

መንግስት የአገር ሀብት የመዘበሩትን ያለርህራሄ ለፍርድ ማቅረቡን እንደሚቀጥል አስታወቀ

0 363

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

 

 

መንግስት መረጃና ማስረጃዎችን መሰረት በማድረግ የህዝብና የመንግስትን ሀብትና ንብረት የመዘበሩ አካላትን ያለርህራሄ ለፍርድ ማቅረቡን እንደሚቀጥል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጸህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

 

ጽህፈት ቤቱ የመንግስትን አቋም በሚተነትነው ሳምንታዊ የአቋም መግለጫው፣ መንግስት በአመቱ መጀመሪያ በህዝብ ተሳትፎና ባለቤትነት የሚካሄድ ሃገራዊ የጥልቅ ተሃድሶ እንቅስቃሴ ማወጁን አስታውሷል፡፡

በተሃድሶ እንቅስቃሴው ልማታዊነትን ከማረጋገጥ በተጓዳኝ የተጠያቂነት አሰራርን ይበልጥ ለማስፈን መንግስት እየሰራ ነው ብሏል መግለጫው፡፡

ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም የመንግስት ሃብትን ለግል ጥቅም በማዋል የተጠረጠሩ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ነጋዴዎችና ደላሎች ሰሞኑን በቁጥጥር ስር መዋላቸውም የዚህ አገራዊ እንቅስቃሴ አካል እንደሆነ ገልጿል፡፡

ይህ እርምጃ ያለ አንዳች – ርህራሄ ተጠናክሮ ይቀጥላል ያለው መግለጫው ፣የተሃድሶው ባለቤትነትና ተዋናይ በመሆን መረጃና ማስረጃ በመስጠትና በመጠቆም የጐላ ድጋፍ እንዲያደርጉ ዜጐችም መንግስት ምስጋናውን አቅርቧል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy