Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

አምስት አርቲስቶች በወንጀልና በሽብርተኝነት ተከሰሱ

1 559

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ሁከትና አመፅን የሚያነሳሱ ዜናዎች፣ ግጭቶችና ሙዚቃ በማዘጋጀት፣ ከኦነግ ባንዲራና ወታደሮች ጋር በማቀናበርና ወደ ውጪ በመላክ በዩቲዮብ ላይ እንዲጫን አድርገዋል የተባሉ 5 የኦሮሞ አርቲስቶችን ጨምሮ 7 ግለሰቦች ትናንት በፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት፣ የሽብርና የወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡

በክስ መዝገቡ ስር የተካተቱት 7 ተከሳሾ አርቲስት መሆናቸው የተመለከተ ሲሆን አሊያድ በቀለ፣ ኢፋ ገመቹ፣ ሃይሉ ነጨ፣ ሴና ሰለሞን፣ ኤልያስ ክፍሉና በግል ስራ እንተዳደራለን ያሉት ሞይቡሊ ሞስጋኑና ቀነኒ ታምሩ ናቸው፡፡

በግለሰቦቹ ላይ ሁለት ክሶች የቀረቡ ሲሆን በአጠቃላይ የክሶቹ ጭብጥ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር የወጣቶች “ሰገሌ ቄሮ” ድምፅ ዜና አዘጋጆችና ዜና አንባቢዎች በሚል ቡድን ራሳቸውን በማደራጀት፣ ዜና በማዘጋጀት ውጪ ላሉት የኦነግ አባሎችና አመራሮች በመላክ፣ በነሱ አማካኝነት ለተለያዩ ማህበራዊ ድረ ገፆች እንዲሰራጩ በማድረግ ህዝብን ለአመፅ በማነሳሳት ስራ ላይ የቆዩ ሲሆኑ በፈፀሙት የሽብር ድርጅት ውስጥ በመሳተፍና የሽብር ተግባር በማሴር፣ በማዘጋጀትና በማነሳሳት ወንጀል መከሰሳቸው ተመልክቷል፡፡

ተከሳሾቹ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን ስለ ሀገሪቱ ፖለቲካ ቃለ መጠይቅ በማድረግ፣ ሁከትና አመፅ የሚያነሳሱ ዜናዎችን በኦሮሚኛና በአማርኛ ቋንቋ አዘጋጅተው በድምፅ በመቅረፅ ማሰራጨታቸውም በክስ መዝገቡ ተጠቅሷል፡፡
ትናንት አርብ ሰኔ 23 በፍ/ቤቱ ክሳቸው በንባብ የተገለፀላቸው ተከሳሾቹ፣ የክስ መቃወሚያቸውን እንዲቀርቡ ለሐምሌ 7 ቀን 2009 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡

admassnews

  1. Aba says

    Please share ESAT lies secret by Abebe Belew: https://www.youtube.com/watch?v=0ECJ0nUm9n8&t=4s

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy