Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ኤች አይ ቪ ቫይረስ ቀድሞ ከታወቀ በበሽታው የመሞት መጠን ይቀንሳል፦ ተመራማሪዎች

0 811

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ሰዎች የኤች አይ ቪ ቫይረስ በሰውነታቸው ውስጥ ቀድሞ መኖሩን ካወቁ በበሽታው የመሞት እድላቸው ዝቅተኛ እንደሚሆን የህክምና ተመራማሪዎች ገለፁ፡፡

አብዛኛውን ጊዜ በኤች አይ ቪ ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች እራሳቸውን የሚያክሙት በሽታው የሰውነት የመከላከል አቅማቸውን ጎድቶ ለተለያዮ በሽታዎች ተጋላጭ ከሆኑ በሃላ እንደሆነ የዘርፉ ተመራማሪዎች ተናግረዋል፡፡

ይህንንም ዝንባሌ ለመቀልበስ የበሽታውን የህክምና አሰጣጥ በመቀየር በዓመት ከ10 ሺህ የሚልቅ የሰው ህይወት መታደግ እንደሚቻል አመልክተዋል፡፡

ተመራማሪዎቹ ሰዎች በኤች አይ ቪ በሽታ መያዛቸውን ቀድመው ካወቁና የተለያዩ አይነት የጸረ ኤችአይቪ መድሃኒቶች ቅልቅል የሆነውን ህክምናን ከጀመሩ በኤች አይቪ ቫይረስ ብቻ ሳይሆን በሳንባ ነቀርሳና በተለያዩ በሽታዎች የሚሞቱ ሰዎችን ቁጥር በእጅጉ መቀነስ እንደሚቻል ነው የተናገሩት፡፡

በዚህም ሳቢያ በበሽታው የተጠቁ ሰዎች የሞት መጠን በ27 በመቶ እንዳሽቆለቆለ ገልፀዋል፡፡

ምንጭ፦ቢቢሲ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy