Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ኖርዌይ ለኢትዮጵያ የ1 ነጥብ 74 ቢሊዬን ብር ድጋፍ አደረገች

0 287

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ኖርዌይ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ እና አየር ንብረት ለውጥ የሚውል የ1 ነጥብ 74 ቢሊዬን ብር ድጋፍ ለኢትዮጵያ ለገሰች፡፡

ድጋፉ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ እና በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ለምታከናውናቸው ሥራዎችና በቀጣይ 4 ዓመታት በሀገሪቱ ለሚተገበረው የኢትዮጵያና ኖርዌይ የአየር ንበረት ለውጥ የአጋርነት ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል ነው፡፡

ፕሮግራሙ የተራቆቱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ የሚያስችሉ ሥራዎች የሚከናወኑበት ሲሆን የደን ሽፋን መመናመንና የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡

በዚህም በደቡብ፣ በጋምቤላና ኦሮሚያ ክልሎች 66ዐ ሺ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ ይከናወናል፡፡

በተመሳሳይም በአማራና ትግራይ ክልሎች ላይ የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ የሚያስችል የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎችም ይከናወናሉ ተብሏል፡፡

ስምምነቱን የተፈራረሙት የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታው አቶ አድማሱ ነበበ በፕሮግራሙ 75 ሺ አባወራዎችና እማወራዎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ገልፀዋል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy