Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የአማራ ክልል ከጎበኝዎች ከ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ

0 428

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በአማራ ክልል የሚገኙ የቱሪዝም መስህቦችን በ2009 በጀት ዓመት ከጎበኙ የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኝዎች ከ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቋል።

ገቢው ከእቅዱ አንፃር የ72 ነጥብ 8 በመቶ አፈፃፀም እንዳለው ተገልጿል።

በበጀት ዓመቱ በክልሉ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችን 9 ነጥብ 6 ሚሊየን ሰዎች መጎብኘታቸው ተነግሯል።

የሀገር ውስጥ ጎብኝዎች ቁጥር ከ9 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ሲሆን ከ1 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል።

ከተለያዩ የውጭ ሀገራት የመጡ ከ105 ሺህ በላይ ጎብኝዎች በክልሉ በነበራቸው ቆይታ 506 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን ቢሮው ገልጿል።

በዙፋን ካሳሁን

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy