Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ሳውዲ ህግ እና ስርአት በሚተላለፉ ግለሠቦች ላይ የሚጣልባቸውን ቅጣት ይፋ አደረገች

0 656

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የሳውዲ አረቢያ መንግስት የምህረት አዋጁ ከተጠናቀቀ በኋላ ህግ እና ስርአቱን በሚተላለፉ ግለሠቦች ላይ የሚጣልባቸውን ቅጣት ይፋ አደረገ፡፡

በቅጣቱ ሀገሪቱን ለመልቀቅ የመውጫ ቪዛ ከወሠዱ በኋላ ሳይጓዙ ለቀሩ ዜጎች የ15ሺ ሪያል ቅጣት፣ ከአሠሪ ውጭ ለግል ጥቅም ሌላ ቦታ ሲሠራ የተገኘ ግለሠብ የ1ዐሺ ሪያል ቅጣት እንዲሁም በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገሪቱ ሲገባ የተገኘ ግለሠብ የ15ሺ ሪያል ቅጣት እና የ1 ወር እስራት የሚጣልበት ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ እያንዳንዳቸው ተይዘው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሡ ይደረጋል ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል በህገወጥ መንገድ የሚኖሩ ግለሠቦችን ሲያጓጉዝ እንዲሁም በማንኛውም ሁኔታ ሲያግዝ የተገኘ ግለሠብ የ25ሺ ሪያል ቅጣት እና የ6 ወር እስራት እንደሚጠብቀው የተገለፀ ሲሆን ለመጓጓዣ የተጠቀመበት መኪናም በመንግስት ውርስ እንዲሆን ክስ ይቀርብበታል፡፡

የመውጫ ቪዛ የተሠጠው ግለሠብ ቪዛው በመቃጠሉ ምክንያት ያልተጓዘ መሆኑን ሪፖርት ያላደረገ 15ሺ ሪያል ቅጣት እንዲሁም የውጭ ሀገር ዜጋ ከሆነ ወደሀገሩ እንዲመለስ ይደረጋል፡፡

የሀጂ እና ዑምራ አገልግሎት ሰጪ ተቋም ለስርአቱ የመጣው ግለሰብ ወደሀገሩ በወቅቱ ሳይመለስ መቅረቱን ለሚመለከተው አካል ያላሳወቀ ከሆነ የ25ሺ ሪያል ቅጣት እንደሚጠብቀው ተቀምጧል፡፡

በእነዚህ እና ሌሎች ምክንያቶች ህግን ተላልፈው በተገኙ ግለሰቦች እንዲሁም ድርጅቶች ጊዜው እየጨመረ በመጣ ቁጥር ቅጣቱም እንደሚከብድ በሳዑዲ አረቢያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያደረሠን መረጃ ያሳያል፡፡

ጉዳይ አስመልክተው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚንስትሩ አማካሪ አምባሳደር ሙሃሙድ ድሪርን በኢቢሲ ስቲድዮ ተጨማሪ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy