Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የፍትህና የጸጥታ አካላት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ ሊሰሩ ይገባል – አቶ ገዱ አንዳርጋቸው

0 458

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ህዝብ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እና የህግ የበላይነትን ለማስፈን የፍትህና የጸጥታ አካሉ ድርሻ ከፍተኛ መሆን እንዳለበት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው አሳሰቡ።

አቶ ገዱ ይህን ያሉት ዛሬ በጎንደር ከተማ ከክልሉ የፍትህ እና ጸጥታ አካላት ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በየደረጃው የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ከፍትህ ስርዓቱ ጋር ተይይዞ በርካታ ጥያቄዎችን እንደሚያነሱ ተናግረዋል።

ከዚህ አንጻርም የፍትህ መጓተት፣ የሀሰተኛ ምስክርና ፍትሀዊ ያልሆኑ ዳኝነቶችን በመቅረፍ ተዓማኒነት ያለው የፍትህ አገልግሎት መስጠት እንዲቻል በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል።

የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሀላፊ አቶ ፍርዱ ቸሩ በበኩላቸው የውይይት መድረኩ የህግ የበላይነትን ለማስፈን እና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ለመጠበቅ፥ በፍትህና በጸጥታ አካሉ ከአሁን በፊት የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍና የተሻሉ አፈጻጸሞችን ለማስቀጠል አላማ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የውይይት መድረኩ ለአምስት ቀናት እንደሚቆይ የጎንደር ፋና ኤፍ ኤም ባልደረባችን ሀይሉ ማሞ ዘግቧል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy