Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ኤች.አይ.ቪ በደማቸው ውሰጥ የሚገኝ መድሃኒቱን እንዲጠቀሙ ለማድረግ የቤት ለቤት ቅስቀሳ በይፋ ተጀመረ

0 1,290

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ኤች.አይ.ቪ በደማቸው ውሰጥ የሚገኝ ዜጎች በአፋጣኝ የፀረ ኤች አይ ቪ መድሃኒት እንዲጠቀሙ ለማድረግ የቤት ለቤት ቅስቀሳና ጥናት በይፋ ተጀመረ።

በኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስተባባሪነት የማህበረሰብ አቀፍ የኤች አይ ቪ ተፅእኖ – በኢትዮጵያ የተሰኘ ዐውደ ጥናት ተከፍቷል።

ጥናቱ ተጨማሪ ስልጠና በተሰጣቸው የህክምና ባለሙያዎች የሚከናወን ሲሆን፤ የህክምና ክትትል የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ከአካባቢው የጤና ተቋም አገልግሎት እንዲያገኙ ሁኔታዎች እንደሚመቻቹም ተገልጿል።

በቤት ለቤት ቅስቀሳ በሚካሄድበት ወቅት በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የኤች.አይ.ቪ ምርመራ እንደሚደረግም ተጠቁሟል።

የዚህ ዓይነቱ ክትትል አዲስ በቫይረሱ የሚያዙ ዜጎችን ቁጥር ለመለየት እንደሚረዳ ተመልክቷል። ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን ተከትሎ የሚመጡ እንደ ጉበትና የአባላዘር በሽታዎች ላይ ምርመራም ይደረጋል።

ከሁሉም አካባቢዎች 25 ሺ ዜጎችን የሚያሳትፈው ይህ ጥናት አገሪቷ የኤች አይ ቪ /ኤድስን በመግታት ረገድ ያለችበትን ደረጃ በጉልህ እንደሚያሳይ በዐውደ ጥናቱ ላይ ተገልጿል።

የጤና ጥበቃ ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ይፍሩ ብርሃነ በዚህ ወቅት እንደገለፁት፤ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ የሚገኝ ሰዎች የፀረ ኤች አይ ቪ መድሃኒቱን በአግባቡ ተከታትለው መውሰድ ይኖርባቸዋል።

መድሃኒቱን በተገቢው መንገድ ተከታትለው መውሰዳቸው ጤናቸውን ከማስተካከሉም በላይ ወደ ሌሎች ሰዎች የማስተላለፍ አቅማቸውን ስለሚቀንስ በአግባቡ መወሰድ እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ አያይዘውም ከዚህ በፊት ሲጠቀሱ የነበሩት “መታቀብ ” መወሰንና መጠቀም” የሚሉት የበሽታው መከላከያ ህጎች በተጨማሪ መመርመርና መታከም የሚሉ ህጎች መካተታቸውን አውስተዋል።

በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አቀፍ ኤች አይ ቪ ተፅዕኖ ጥናት ፕሮጀክት ኃላፊ ዶክተር ዴቪድ ሁዝ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ቫይረሱ በደሙ ከሚገኝባቸው ሰዎች መካከል 60 በመቶ የመድሃኒት ተጠቃሚ ማድረጓን አድንቀዋል።

ኢትዮጵን ጨምሮ  በማህበረሰብ አቀፍ ኤች አይ ቪ ተጽዕኖ ላይ ጥናት ለሚያደርጉ 14 አገሮች ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁን የሰባት አገሮች መረጃ መሰብሰቡን ተናግረዋል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy