Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ከመተማ ወደ ጎንደር ከተማ ሊገቡ የነበሩ የጦር መሳሪያዎች ተያዙ

0 1,576

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ከመተማ ወደ ጎንደር ከተማ በድብቅ ሊገቡ የነበሩ 21 ሽጉጦችና ከ15 ሺህ በላይ ጥይት መያዙን በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የጎንደር ጉምሩክ መቅረጫ ጣቢያ አስታወቀ።

በጎንደር ጉምሩክ መቅረጫ ጣቢያ የሰራባ ኬላ አስተባባሪ ኮሎኔል ብርሃነ መብራት ለእንደተናገሩት፥ የጦር መሳሪያና ጥይቶቹ የተያዙት ከጭልጋ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው ሰራባ በተባለው የመቆጣጠሪያ ኬላ ነው።

የጦር መሳሪያዎቹንና የክላሽ ጥይቶቹን በድብቅ ጭኖ የተገኘው የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 2-12155 አዲስ አበባ የሆነ ፒካፕ ተሸከርካሪ ሲሆን በመኪናው ውስጥ የነበሩ አራት ተጠርጣሪዎችም በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ከትናንት በስቲያ ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመተባበር በተደረገው ጥብቅ ቁጥጥርና ፍተሻ የተያዙት የጦር መሳሪያዎችና ጥይቶች በመኪናው አካል ላይ በረቀቀ መንገድ ተበይደው በተዘጋጁ ስውር ቦታዎች ተቀምጠው የተገኙ ናቸው።

“ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር በአካባቢው እየተስፋፋ መጥቷል” ያሉት የኬላው አስተባባሪ፣ በዚህ ተግባር ላይ የሚሳተፉ ወንጀለኞችን በማጋለጥና ጥቆማ በመስጠት ሕብረተሰቡ የጀመረውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

ከታህሳስ እስከ የካቲት ወር 2010 ዓ.ም ባሉት ሦስት ወራት ብቻ በሰራባ ኬላ 7 ሺህ ጥይቶች፣ 25 ሽጉጦችና ሁለት ክላሽን ኮቭ ጠብመንጃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኮሎኔል ብርሃነ ተናግረዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy