Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የሰላምና የልማት ህዝባዊ ኮንፍረንስ በመቐለ ሊካሄድ ነው

0 324

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ከሁሉም ክልሎች የተወጣጡ የማህበረሰብ ተወካዮች የሚሳተፉበት የሰላምና የልማት ህዝባዊ ኮንፍረንስ ከመጋቢት 19 2010 ዓ.ም ጀምሮ በመቐለ ከተማ እንደሚካሄድ ተገለጸ።

በትግራይ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የሚዲያዎች አቅም ልማት ግንባታና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ግርማዬ እንዳሉት፥ ለ4 ቀናት የሚካሄደው የኮንፍረንሱ ዓላማ የህዝቦችን አንድነት ለማጠናከር ነው።

የኮንፍረንሱ ተሳታፊዎች በቆይታቸው በሰላም፣ በልማትና በዴሞክራሲ ግንባታ ዙሪያ እንደሚወያዩ ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።

የክልሉ መንግስት ባዘጋጀው በዚሁ ኮንፍረንስ ከ2 ሺህ 500 በላይ የማህበረሰብ ተወካዮች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

ምንጭ፦ ኢዜአ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy