Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሟላ ፖሊሲን ይዘው በመቅረብ ብቁ ተፎካካሪ መሆን እንደሚገባቸው ገለፁ

0 746

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለህዝቡ አማራጭ ሆኖ ለመገኘት ለሚያደርጉት ጥረት ምስጋና አቀረቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በብሄራዊ ቤተመንግስት ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር ለእራት ተቀምጠዋል።

በዚሁ ስነ ስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በሀገሪቱ ለምርጫ እና ፉክክር ያለበት ፖለቲካ እንዲፈጠር ምህዳሩን የማስፋት ስራ እንደሚከናወን ተናግረዋል።

ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሟላ ፖሊሲን ይዘው በመቅረብ ብቁ ተፎካካሪ መሆን እንደሚገባቸውም ነው ያሳሰቡት።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የዜሮ ድምር ውጤት ፖለቲካንም በመንቀፍ ይህ ሀገሪቱን ዋጋ እንደሚያስከፍል ነው ያነሱት።

በብሄራዊ ቤተመንግስት በተካሄደው የእራት ግብዣ ላይ ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች በተጨማሪ ጥሪ የተደረገላቸው የሀይማኖት አባቶች እና ታዋቂ ግለሰቦች ተገኝተዋል።

Photo credit: Addis fortune

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy