Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ለ286 የአውሮፕላን አብራሪዎች ፍቃድ መስጠቱን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ

0 368

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በተያዘው በጀት ዓመት ለ286 አዳዲስ የአውሮፕላን አብራሪዎች ፍቃድ መስጠቱን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ።

ባለሰልጣኑ ፍቃዱን የሰጠው በበጀት አመቱ ዘጠኝ ወራት ነው።

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የማስታወቂያና የህዝብ ግንኙነት ስራ አስኪያጅ አቶ አንሙት ለማ ለፋና ብሮድካስቲግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ ፍቃዱ የተሰጠው በተለያዩ ዘርፎች ነው።

በዚህም መሰረት ፍቃድ የተሰጣቸው፥ 87 የትራንስፖርት አውሮፕላን አብራሪዎች፣ 48 የንግድ አውሮፕላን አብራሪዎች፣ 8 የግል አውሮፕላን አብራሪዎች፣ 111 የተማሪ አውሮፕላን አብራሪዎች ናቸው።

እንዲሁም በሁለት ዘርፍ የትራንስፖርትም የንግድም አውሮፕላን ለሚያበሩ 32 አብራሪዎችም ፍቃድ መሰጠቱን አቶ አንሙት አስታውቀዋል።

ተጨማሪ 397 የ‘‘A’’ ደረጃ ግራውንድ ቴክኒሻን ፍቃድም ተሰጥቷል።

በታሪክ አዱኛ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy