Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የጨፌ ኦሮሚያ 7ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችንና ረቂቅ አዋጆችን በማፅደቅ ተጠናቀቀ።

0 434

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የጨፌ ኦሮሚያ 7ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችንና ረቂቅ አዋጆችን በማፅደቅ ተጠናቀቀ።

ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የጨፌው መደበኛ ጉባኤ በዛሬው እለት ተጠናቋል።

ጉባኤው በዛሬው ቆይታ አቶ ደሳ ቡልቻ ነሞምሳን የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት እንዲሁም አቶ ማህመድኑሬ ጎበናን ምክትል ፕሬዚዳንት አድርጎ ሾሟል።

ወይዘሮ ማህቡባ አደም የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ፣ አቶ ወርቁ ጋቸና የኦሮሚያ ክልል ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ ዋና ዳይሬክተር እንዲሁም አቶ አዲሱ አረጋን የኦሮሚያ ክልል ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ የቦርድ ሰብሳቢ በማድረግ ሾሟቸዋል።

ከዚህ ባለፈም በ2002 ዓ.ም የክልሉን የፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ ለማሻሻል የወጣውን ረቂቅ አዋጅ እና የኦሮሚያ ክልል ብሮድካስቲንግ ኔትወርክን ዳግም ለማቋቋም የወጣውን አዋጅም አጽድቆታል።

 

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy