Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በ630 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው አባይ ህትመትና ወረቀት ፋብሪካ ተመረቀ

0 2,752

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በ630 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው አባይ ህትመትና ወረቀት ፓኬጂንግ ፋብሪካ በዛሬው እለት ተመረቀ።

ፋብሪካው በአማራ አቀፍ ልማት ማህበር (አልማ) እና በአማራ ደን ኢንተርፕራይዝ አማካኝነት በጋራ የተገነባ ነው።

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ፋብሪካውን ተገኝተው መርቀዋል።

ፋብሪካው ለህትመትና ወረቀት ስራው ጥሬ እቃዎቹን በሀገር ውስጥ የሚጠቀም መሆኑም በዚህ ወቅት ተገልጿል።

የፋብሪካው መገንባትም በሀገሪቱ ያለውን የህትመትና የወረቀት ዋጋ ማሻቀብ ይቀርፋል ተብሎ ይጠበቃል።

ባህር ዳር ከተማ አባይ ማዶ አካባቢ የተገነባው ፋብሪካ ግንባታ በሶስት አመታት ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀ ነው።

መረጃው የአማራ መገናኛ ብዙሃን ድርጅት ነው።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy