Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በኢትዮጵያ የተጀመረውን የለውጥ እንቅስቃሴ በተጠናከረ የአመራር ብቃት ለመደገፍ እንሰራለን – የብዓዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ

0 751

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በኢትዮጵያ የተጀመረውን የለውጥ እንቅስቃሴ በተጠናከረ የአመራር ብቃት ለመደገፍ እንደሚሰሩ የብዓዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ድርጅቱ በመጪው መስከረም ወር በሚካሂደው 12ኛው ጉባዔ ለውጡን ማስቀጠልና የህዝብ ፍላጎት ማሟላት የሚችሉ ጠንካራ አመራሮችን እንደሚሾም ገልጿል፡፡

በጽህፈት ቤቱ የገጠር ፖለቲካ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ምግባሩ ከበደ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ድርጅቱ በቀሪ የክረምት ጊዜያት በሚያከናውናቸው ተግባራትና የቀጣይ ጉባዔ አጀንዳዎች ዙሪያ ውይይት እያካሄደ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ብዓዴን ድርጅት ብቻ ሳይሆን የክልሉ ህዝብ መሪ በመሆንም በሀገራችን የተጀመረውን ለውጥ ደግፎ ከግብ ለማድረስ ጠንክሮ ይሰራል ብለዋል፡፡

የህዝቡ ጥያቄዎች በአፋጣኝ እንዲመለሱና የህግ የበላይነት እንዲከበር ድርጅቱ ከምንጊዜውም በተሻለ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የተገለጸ ሲሆን የድርጅቱን አቅም የሚጠናክርና ለውጡን ለማስቀጠል የሚያስችሉ አመራሮች ተመርጠው በቀጣይ ጉባዔ እንደሚሾሙ ታወቋል፡፡

በጉባዔው ላይ መሻሻል የሚገባቸው የድርጅቱ መተዳደሪያ ደንቦችና የአሰራር መመሪያዎች ማሻሻያ እንደሚደረግባቸውም ተገልጿል፡፡

በድርጅቱ ውስጥ የሚታየውን ጉራማይሌ የሆነ የአመራር ብቃት ለማስተካከልም በትኩረት እንደሚሰሩ አቶ ምግባሩ ተናግረዋል፡፡

በመስከረም ወር የሚካሄደው ጉባዔም በአጀንዳዎቹ ዙሪያ ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡

fbc

 

በሙሉጌታ ደሴ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy