Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የደቡብ ሱዳን አማፂ ቡድን መሪ ሪክ መቻር አዲሱን የሰላም ስምምነት ውድቅ አደረጉ

0 329

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የደቡብ ሱዳኑ አማፃ ቡድን መሪ ሪክ ማቻር በሀገሪቱ ያለውን የእርስ በእርስ ግጭት ፍፃሜ ያበጃል ተብሎ የተጠበቀውን የሰላም ስምምነት ውድቅ ማድረጋቸውን  የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ባለፈው ወር የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪርና ሪክ ማቻር የተኩስ አቁም  እና የስልጣን መጋራት እንዲኖር የሚያስችል ስምምነት መፈራረማቸው የሚታወስ ነው።

ሆኖም ሪክ ማቻር አዲስ የተዘጋጀውን የሰላም ስምምነት ውድቅ ያደረጉ ሲሆን፥ ይህም ወደ ሙሉ ስምምነት ለመድረስ የሚደረገው ጥረት አዳጋች እንደሆነ የሚያሳይ ነው ተብሏል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አል ዲርዲር መሀመድ፥ ዋነኛው የአማፂ ቡድን መሪ ሪክ ማቻርን ጨምሮ ሌሎች አማፂ ቡድኖች ከተለያዩ ጥቃቶች እንዲቆጠቡ የሚያስችለውን ስምምነት ውድቅ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።

በደቡብ ሱዳን ያለው የእርስ በእርስ ግጭት ሀገሪቱ ነፃነቷን ከአወጀች ሁለት አመታት በኋላ በፈረንጆቹ 2013 የተጀመረ ሲሆን፥ 12 ሚለየን የሚሆነው የሀገሪቱ ዜጎች ከመኖሪያቸው ቄያቸው እንዲፈናቀሉ ምክንያት ሆኗል።

ምንጭ፥ ሲጂቲኤን

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy