Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ እየወሰዱ ያለውን የለውጥ እርምጃ አደነቁ

0 716

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ እየወሰዱ ያለውን የለውጥ እርምጃ አደነቁ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2010 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶከትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ በሀገሪቱ እየወሰዱ ያለውን የለውጥ እርምጃ አድንቀዋል።

ፕሬዚዳንት ኢማኑኤክል ማክሮን ይህንን የተናገሩት በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው የተሾሙት ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር አሊ ሱሌይማን የሾመት ደብዳቤያቸውን ባቀረቡላቸው ጊዜ ነው።

ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮንም አምባሳደር አሊ ሱሌይማንን በኤሊሴ ቤተ መንግስት ተቀብለው አነጋግረዋል።

በዚሁ ወቅትም ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አምባሳደር አሊ ሱሌይማንን ያመሰገኑ ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን ለውጥም አድንቀዋል።

ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አክለውም፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ በሀገሪቱ እየወሰዱት ያለው የለውጥ እርምጃ የሚደነቅ መሆኑን ገልፀዋል።

ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ እያመጧቸው ላሉ ለውጦችም አድናቆታቸውን እንዲያስተላልፉላቸውም ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለአምባሳደር አሊ መናገራቸውን በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የፊታችን ጥቅምት ወር 2011 ዓ.ም በፈረንሳይ ፓሪስ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አበይ ወደ ፓሪስ የሚያቀኑትም በፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ገብዣ ነው።

ፕሬዚዳንት ማክሮን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አሕመድ ከዚህ ቀደም በስልክ መወያየታቸው ይታወሳል።

በውይይታቸውም ፕሬዚዳንት ማክሮን አሁን ላይ በኢትዮጵያ እየታዩ ያሉ ለውጦችን ፈረንሳይ የምትደግፍ መሆኗንም ተናግረዋል።

ፕሬዚዳንት ማክሮን በወቅቱ ኢትዮጵያና ኤርትራ ለሰላም በደረሱት ሥምምነት የተሰማቸወን ደስታ መግለፃቸውም ይታወሳል።

በሙለታ መንገሻ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy