Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ፍርድ ቤቱ አቶ አብዲ መሃመድ ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቀደ

0 810

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ፍርድ ቤቱ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሐመድ ዑመር ጨምሮ በአራት ተጠርጣዎች ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ለፖሊስ ፈቀደ፡፡

የፌደራል መርማሪ ፖሊስ ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ በአራት ተጠርጣሪዎች ላይ የ18 ሟቾችን እና የ438 አካል ጉዳት የደረሰባቸውን ግለሰቦች የህክምና ማስረጃ መሰብሰቡንና ዘጠኝ የጦር መሳሪያዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ለችሎቱ አብራርቷል፡፡

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት የመርማሪ ፖሊስ የተሰጠው ጊዜ የሰራቸው ስራዎች እና ቀሩኝ ያላቸው ምርመራዎች እንዲሁም የተጠርጣሪዎችን አስተያየት አዳምጧል፡፡

በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ ለመርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ የ10 ቀን የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል፡፡ 

FBC

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy