Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ወልቃይት ጠገዴ በትግራይ ክልል ውሥጥ የገባው ዛሬ አይደለም

0 31,490

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ወልቃይት ጠገዴ በትግራይ ክልል ውሥጥ የገባው ዛሬ አይደለም፣ ከ 27 ዓመታት በፊት ነው። ራያ ትግራይ የሆነው በአብይ አይደለም በመለስ ነው።

ከሞት ባይኖር ሲደልል

አማራው የትግራይ ሕዝብ ጠላት ተደርጎ ሲሳል፣ አማራው የኦሮሞው ገዳይ ሲባል፣ አማራው የኤርትራ ሕዝብ ጠላት ሲባል አማራው የት ነበር? ባላጠፋው ስወነጀል ምነው አማራው አልፎከረ? ዛሬ ግን በገሀድ “ በአፈሙዝ መብቴን አስከብራለሁ” ያለው በፍቅር እንኑር የሚል ሲመጣ ነው። መለስ ዜናዊን ለ20 ዓመታት የረባ ተቃውሞ ያላደረገ አማራ፣ ዛሬ መሣሪያ አነሳለሁ አትንኩኝ ብሎ ወጣ። ለመሆኑ መብታችንን በኃይል የምናስመልሰው ዛሬ ነው? ያኔ መብታችን በኃይል ሲወሰድ ኃይላችን የት ነበር? መለስ ከመሞቱ በፊት በኃይል ተነጠቅን የምንለውን ጠገዴን ለምን አላስመለስንም? የዛሬው የጎንደር ጥያቄው ብቻ አግባብ ሊሆን ይችላል። በተቃውሞ፣ በኃይል፣ በአፈሙዝ፣ የሚሉት አባብሎች ግን ተገቢ አይድደሉም። እንኳን እንደ አብይ አይነት በፍቅር እንኑር የሚለው ቀርቶ፣ የተለካ ድሞክራሲ ለሰጠን መለስ ዜናዊን እንኳን በኃይል ሳይሆን በኃሳብ ማሸነፍ ያለብን ዘመን ላይ ነን። አማራው በኢትዮጵያ ጥላ ስር እንጂ በአማራ ብሔር ስር ሲሰባሰብ አዘንኩ። ትውልዴ ከጎንደር ወጣ ብላ የምትገኘው ሸንበቂት ቢሆንም በአማራ ስር አልደራጅም። አማራ ወይንም ሞት ከሚሉጋ ሕብረት የለኝም። ዛሬ ወልቃይት የኢትጵያዊ ሁሉ እንጂ ወልቃይት አማራም ትግራይም አይደለም ብዬ ማሰብ ነው የምፈልገው። ጠገዴ የትግራይ፣ ጠገዴ የከንባታ፣ ጠገዴ የኦሮሞ፣ ጠገዴ የኔም የሁላችን ነው። በመንደር እና በብሔር አልደራጅም። ድርጅቴ ኢትዮጵያ፣ ማኅበሬ ኢትዮጵያ፣ ብሔሬ ኢትይጵያ ናት፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy