Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

‹‹ሀገርን መወከል ከባድ ሃላፊነት ነው›› የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ

0 943

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴት ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነ ገበየው አዲስ ለተሸሙትና ለነባር አምባሳደሮች በተዘጋጀው ስልጠና መድረክ ላይ ሀገርን መወከል ከባድ ሃላፊነት መሆኑን ተናገሩ፡፡

ይህ ስልጠና በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ የሚያተኩር ሲሆን በዋናነት ግን የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም በማስከበር ዙሪያ የሚጠበቅባቸው ሀላፊነትና ለዜጎች በሚሰጠው ትኩረት ላይ የሚያተኩር ይሆናል፡፡

ዶ/ር ወርቅነ ስልጠናውን ባስጀመሩበት ወቅት ሁሉም አምባሳደሮች ለሀገራቸው ቅድሚያ መስጠት እንደሚገባቸው በማሳሰብ በሚሄዱባቸው ሀገራት የሀገራቸውን ባህልና ወግ በሚገባ ማስተዋወቅና የሚፈጥሩት ዲፕሎማሲ ከእጅ መጨባበጥ ያለፈ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

በዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዙሪያ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ከተለያዩ ተቋማት በተውጣጡ ምሁራንና የሙያው ጠበብቶች ስልጠናውን የሚሰጡ ይሆናል ፡፡

ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ እስከ የካቲት 1ቀን2011 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሲሆን በመጨረሻ ቀን የሁሉም አምባሳደሮች ባሎችና ሚስቶች ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy